ልጥፎች

ኩነኔ የለብንም

ምስል
  ኩነኔ የለብንም ‘ኩነኔ የለብንም’ የሚለው ቃል ምን ማለት ነው?  የምንናገረው ስለ እግዚአብሔር ቁጣ እና የሲኦል ቅጣት ነው ወይንስ ይህ የተለየ ትርጉም አለው?  እንግዲህ፣ ‘ምንም ኩነኔ የለብንም’  ይሄ ጉዳይ ከሁለት ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ ነው።  የመጀመሪያው ሁኔታ ‘በክርስቶስ’ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ‘መንፈስን የሚመላለሱ’ ነው።  ቀደም ባሉ ምዕራፎች በሮሜ ውስጥ ‘በክርስቶስ’ የሆነ ሰው (የጸደቀ) ከቁጣና ከገሃነም እንደዳነ ሮሜ.5፡18 የሚለውን መረዳት አለብን።  ስለዚህም ‘ኩነኔ የለብንም’ በእርግጠኝነት ከቁጣ እና ከገሃነም ነጻ መውጣትን ያካትታል።  ነገር ግን በሁኔታ ሁለት ላይ በመመስረት፣ ይህ አባባል ራስን ከመኮነን ነጻ እንደሆነ ልንረዳው ይገባል።  ላብራራ። ምን ያወግዛል?  ሕጉ።  በሮሜ 7፡7-25 ጳውሎስ እንደጠቀሰው በእኛ ውስጥ ሞትን የሚሠራ እና በደልን እና መከራን የሚያመጣ ህግ ነው።  ነገር ግን፣ ከህግ ነጻ መውጣት ምን ማለት እንደሆነ ስንማር፣ እና ከመንፈስ ለመከተል እምነትን ስንለማመድ  ከመጽደቅ ቅጽበታዊነት በተለየ መቀደስ የሕይወት ረጅም ጉዞ ነው ይህም ቅድስና በሂደት የሚመጣ ነው ማለት አይደለም የተቀበልነውን ህይወት በኑሮ ከመግለጥ ጋር በተያያዘ እንደሆነ አንባቢው ልብ ይበል።  ትምህርታችንን ለእውቀት እንማራለን እንጨምራለን እና አእምሯችን የበለጠ ሲታደስ በውስጣችን ወዳለው የክርስቶስ አምሳል ወይም አዲሱ ሰው እንለወጣለን።  ጳውሎስ የሚከተለውን ጽፏል። ሮሜ 6፡16-18 ለመታዘዝ ባሪያዎች እንድትሆኑ ራሳችሁን ለምታቀርቡለት ለእርሱ ለምትታዘዙለት ባሪያዎች እንደ ሆናችሁ አታውቁምን?  ኃጢአት ለ...

እምነት መገኛው ቃሉ ነው

ምስል
 የእምነት ፍቺው በሥጋዊም ሆነ በመንፈሳዊ መልኩ ወጥነት ያለው ነው፣ነገር ግን የእምነት መሠረት፣ ወይም አመጣጥ፣ በእያንዳንዱ ሁኔታ የተለየ ነው።  በተፈጥሮው ዓለም እምነት በአንድ ነገር እውቀት እና ልምድ ላይ የተመሰረተ ነው, እናም አንድ ሰው የሚፈልገውን ውጤት ተስፋ በማድረግ በእሱ ላይ እምነት ይጥላል.  መጽሐፍ ቅዱሳዊ እምነትን በተመለከተ፣ ምንጩ በተጻፈው በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ብቻ ነው።        ”ሮሜ 10፥17                                                                                           “እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው።              በተለይም በጳውሎስ መልእክቶች በተሰጠን የአገልግሎት ዘመን እና ትምህርት ውስጥ፣ በቃሉ ውስጥ ካሉት ሌሎች ከመንፈሳዊ መርሆዎች ጋር የሚስማማውን ሌላ ጊዜያዊ እውነትን ጨምሮ  ትምህርታችን እምነታችን ያ አስተምህሮ በሚናገረው ላይ ተመስርቷል ለውጤቱም ያለን ተስፋ በፍላጎታችን ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ትምህርታችን በሚወስነው ላይ ነው።  የመጽሐፍ ቅዱሳዊው ትምህርታችን ውጪ ያለው  እምነት ቀላል ከንቱነት፣ ወደ ውሸት፣ ...

የእስራኤል እና የክርስቶስ አካል ልዮነት

ምስል
 የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተ ክርስቲያን ከአይሁድና ከአሕዛብ የተዋቀረች አዲስ ፍጥረት እንጂ አሥራ ሁለት ነገድ የላትም።   ጀስቲን ጆንሰን እንደተየበው በ ይሳቅ አሰፋ የተተረጎመ  መጽሐፍ ቅዱስ ስለ አሥራ ሁለት ነገዶች ሲናገር፣ ስለ አንድ አካል ቤተክርስቲያን አይናገርም ለያይቶ ነው ያስቀመጣቸው  (ሮሜ 12፡5፣ ኤፌ 1፥22-23 እና 4፡4)።  አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች  የእስራኤል ብሔር የሆኑ አሥራ ሁለት ቤተሰብ ነገዶች ነበሩ።  እነዚያ ነገዶች ከአሥራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች የመጡ ናቸው  -(ዘፍ 49፡28)።  እስራኤል ሕጉን ሁሉ ለማድረግ በተስማሙ ጊዜ፣ ሙሴ ለመታሰቢያ የሚሆን አሥራ ሁለት ሀውልቶች  ሠራ፤ ለእያንዳንዱ የእስራኤል ነገድ አንድ ም። “ሙሴም የእግዚአብሔርን ቃሎች ጻፈ ማለዳም ተነሣ፥ ከተራራውም በታች መሠዊያን፥ አሥራ ሁለትም ሐውልቶች ለአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ ሠራ።”   — ዘጸአት 24፥4  በአሮን ኤፉድ ውስጥ እንደ አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ አሥራ ሁለት ድንጋዮች ነበሩ።  “የዕንቈቹም ድንጋዮች እንደ እስራኤል ልጆች ስሞች አሥራ ሁለት ይሆናሉ፤ በየስማቸውም ማተሚያ እንደሚቀረጽ ይቀረጹ፤ ስለ አሥራ ሁለቱ ነገዶችም ይሁኑ።”   — ዘጸአት 28፥21 መልካሙንም ዱቄት ወስደህ አሥራ ሁለት ኅብስት ጋግር በአንድ ኅብስት ውስጥ ከመስፈሪያው ከአሥር እጅ ሁለት እጅ ይሁን። እነዚህንም ስድስት ስድስቱን በሁለት ተርታ አድርገህ በእግዚአብሔር ፊት በጥሩ ገበታ ላይ አኑራቸው።ለእግዚአብሔርም ለእሳት ቍርባን በእንጀራው ላይ ለመታሰቢያ ይሆን ዘንድ በሁለቱ ተርታ ላይ ጥሩ ዕጣን አድርግ።በእግዚአብሔር ፊት ሁልጊዜ በሰንበት ቀን ሁሉ ...

ለኃጢአት ሞተናል

ምስል
 ሮሜ 6 ¹ እንግዲህ ምን እንላለን? ጸጋ እንዲበዛ በኃጢአት ጸንተን እንኑርን? አይደለም። ² ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት አድርገን በእርሱ እንኖራለን? Romans 6 (KJV) ¹ What shall we say then? Shall we continue in sin, that grace may abound? ² God forbid. How shall we, that are dead to sin, live any longer therein? "ለኃጢአት የሞትን እኛ ወደ ፊት እንዴት በእርሱ እንኖራለን?" የሚለው ሐረግ የአጻጻፍ ጥያቄ ነው።  ጳውሎስ መልስ እየጠበቀ አይደለም ነገር ግን ክርስቶስን የተቀበሉ እና 'ለኃጢአት የሞቱ' ሰዎች በኃጢአት መኖራቸውን መቀጠል እንደሌለባቸው God forbid እግዚአብሔር ይሄንን ከልክሏል ይላል!!! ይህን በመግለጽ በሮም ላሉት አማኞች እውነቱን ለማጉላት አንድ ነጥብ እየተናገረ ነው።  እውነታው ግን ለኃጢአት የሞተ ሰው (በክርስቶስ ላይ ባለው እምነት) በኃጢአት ውስጥ መኖርን ለመቀጠል አቅም የለውም አቅም (ፀጋ) ያለው በፅድቅ ለመኖር ነው።  ለውጥ በአማኝ ሕይወት ውስጥ መከሰት አለበት፣ ከኃጢአተኛ ምግባራት እየራቁ እና በክርስቶስ ባለው አዲሱ ማንነታቸው እንደሚገባ እየኖሩ ለጌታ እንዲኑ ይመክራል። ዛሬም እኛ ይህም በራሳችን ጥንካሬ ልናደርገው የምንችለው ነገር አይደለም።  የእግዚአብሔር ሥራ ፀጋ ነው፣ በተጻፈ ቃሉ፣ የሚያጥበን እና አእምሮአችንን የሚያድስ፣ እና በህይወታችን፣ በንግግራችን፣ በሃሳባችን፣ በድርጊታችን እና በህይወታችን ምላሾች ላይ ተጽእኖ ማድረግ ይጀምራል።  ለሥጋዊ ተፈጥሮአችን መሞትን እንድንጀምር እና የክርስቶስን ባሕርይ እንድንለብስ የሚያደርገን የተጻፈ ቃል ነው። ፀጋ ይብዛላችሁ ?...

እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው

ምስል
 አንዴ ከዳንክ እግዚአብሔር ከአንተ የሚፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው።  እውነትን ወደ ማወቅ እንድትመጣ ይፈልጋል!  እግዚአብሔር ቃሉን እንድትማር ይፈልጋል።  ቃሉ እንዲሞላህ፣ እንዲያጠግብህ፣ ተጽዕኖ እንዲያሳድርብህ እና ከአንተ እንዲወጣ ይፈልጋል።  በቃሉ እውቀት ከኖርክ፣ እና ሀሳብህ፣ ንግግርህ፣ ድርጊትህ እና ምላሽህ፣ እና ውሳኔዎችህ በቃሉ ተጽእኖ ስር ከሆኑ እና በቃሉ መሰረት፣ በመንፈስ እየተመላለስክ ነው።  ኢየሱስም _“ቃሌ መንፈስ ነው ሕይወትም ነው” ብሏል።_ የእግዚአብሔር ቃል የሕይወትህ ሁሉ ምንጭ ሲሆን በመንፈስ ትመላለሳለህ። በቃሉ እውቀት እየተነካ ነው።  የእግዚአብሔርን ቃል ባወቅህ መጠን ፈቃዱንና መንገዶቹን በይበልጥ ባወቅህ መጠን እና የበለጠ ስትረዳ በመንገዱ ውስጥ ትሄዳለህ።  ይህ ሲሆን የሥጋን ሥራ መናቅ ትጀምራለህ። “እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞቱ ዘንድ አላችሁና፤ በመንፈስ ግን የሰውነትን ሥራ ብትገድሉ በሕይወት ትኖራላችሁ።”    ሮሜ 8፥13 “ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።”    ገላትያ 5፥16 ቃሉ ከአንተ በወጣ ቁጥር የክርስቶስ ህይወት ከህይወትህ ላይ ይፈሳል።  ኃጢአትን ማሸነፍ የሚቻለው በዚህ መንገድ ነው።  ሥጋን ማሸነፍ የሚቻለው በዚህ መንገድ ነው።  ህግን በማዘጋጀት አይደለም.  በዲሲፕሊን አይደለም። በራስ ፈቃድ እና በሰዎች ጥንካሬ አይደለም። ይህ ሁሉ ይከሽፋል እና ዞሮ ይኮንናል እናም በአንተ ውስጥ ላለው የመንፈስ አሠራር ሞትን ያመጣል  ፊደል ይገድላል መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል።  ስለዚህ አሁንም እላለሁ እግዚአብሔር ከአንተ ምን ይፈ...

የእምነት ፅድቅ

ምስል
 ሮሜ 4 ²⁰-²¹ ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ²² ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። ²³ ነገር ግን፦ ተቈጠረለት የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤ ²⁴-²⁵ ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው። እንዴት ድንቅ ቃል ነው።  አብርሃም እግዚአብሔር የተናገረውን እንደሚፈጽም በማመን በእምነት አልጠራጠረም አጥብቆ ተረድቷል ስለዚህም እግዚአብሔር አብርሃምም ጽድቅ ሆኖ ተቆጥሮለታል።  የእኛም እንደዚሁ ነው።  እኛን ለመጽደቅ በክርስቶስ የመስቀል ሥራ ላይ የማያወላውል እምነት ሊኖረን ይገባል ምክንያቱም የእግዚአብሔር ኃይል ክርስቶስን ከሙታን አስነስቶ እኛን መዳን የሚገኝበትን ይህ ጽድቅ እንደተቆጠርን ያረጋግጥልናል። እግዚአብሔር የታመነና የገባውን ቃል ለማድረግ የሚችል ነው።  ሃሌ ሉያ! ፀጋ ይብዛላችሁ 🥰🙏 ወንድማችሁ ይሳቅ

በአእምሮህ ውስጥ ምን አለ?

ምስል
ይህ የእምነት እና የክርስትና_ሕይወት ቁልፍ ነው።  የእምነታችሁ እና የክርስቲያናዊ ኑሮዎ ዋና ነገር በአእምሮአችሁ ውስጥ ባለው ነገር ላይ የተመሰረተ ነው። በእግዚአብሔር ቃል በሚታደስ እና በመንፈሳዊ ጥበብ እ እወነት መርህ ላይ በተመሰረተ አእምሮ እየሰራችሁ ነው ወይንስ በአለማዊ እውቀት እና ከንቱነት ላይ በተመሠረተ አእምሮ እየሰራችሁ ነው? በትክክል ስለተከፋፈለው ቃል እውቀት ማግኘት የህይወት እና የመንፈሳዊ ጥንካሬ ዋና አካል ነው። እምነትን ይጨምራል፣ በረከትን ይመግባችኋል፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ይሞላችኋል፣ ለጌታ እንደሚገባ እንድትመላለሱ ኃይል ይሰጣችኋል፣ ከጠላት ጋር የምትዋጋበት ትጥቅ ነው። የመንፈሳዊ እወነት እውቀት መጨመር ከሁሉም በላይ አስፈላጊው ነገር ነው ግን በብዙ ክርስቲያኖች ሕይወት ውስጥ በጣም ዝቅተኛ ዋጋ ያለው ተግባር ሆኗል። መጽሐፍ ቅዱስ ለአእምሮ የሚሰጠውን ግምትና በመንፈስና በእውነት መታደስ ያለውን አስፈላጊነት ይህ ነው የማይባል ጠሊቅ ነው ቃሉን እንያዝ ቃሉን በክርስቶስ ኢየሱስ አእምሮአችንን የሚያድስ ነው። ፀጋ ይብዛላችሁ 🥰🔥 ወንድማችሁ ይሳቅ

ክፍል 2: የተቀደሰ (በህይወቱ የዳነ)

'በህይወቱ የዳነ' ለኃጢአት ለመሞት እና ለአዲስ ሕይወት የማነፅ ሂደታዊ (ተራማጅ) ሥራ ነው ሮሜ 6፡4 ።  እንደ መጽደቅ ያለ ፈጣን የቅፅበት ልውጠት  ሳይሆን አእምሮን የማስተማር እና የማደስ ሂደት ነው።  እሱም በትክክል የተከፋፈለውን የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናት እና ከትምህርታችን ጋር በጳውሎስ ሥርዓተ ትምህርት ከሮሜ እስከ 2ኛ ተሰ በሥጋችን ያለው ኃጢአት ባህሪ ይገፈፍ ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን።  ለጽድቅ እንድንሰጥ ራሳችንን ለኃጢአት እንደሞትን ልንቆጥር ይገባናል።  በአዲስ ህግ ስር መኖር እና መስራት እንድንችል በክርስቶስ አካል ለህግ የሞትን መሆናችንን ማወቅ አለብን።  ለእግዚአብሔር በመንፈስ አዲስ ፍሬ እናፈራ ዘንድ የሕይወት መንፈስ ሕግ ይገዛናል።  በሕይወቱ የዳነ በክርስቶስ ከሕፃንነት ወደ እግዚአብሔር ልጅ የማደግ ሂደት ነው።  ትምህርቱን በመረዳት እና ወደዚያ የፍቅር እየተጋን የመንፈስ ፍሬ በእኛ እንዲሰራ የመፍቀድ የእምነት ስራ ነው። ፀጋ ይብዛላችሁ 🥰🙏 ወንድማችሁ ይሳቅ

ጸድቀናል (ታረቅን)

 ክፍል 1: ጸድቀናል (ታረቅን) መጽደቅ የነፍሳችንን አሁናዊ አቋም መቤዠት ይመለከታል።  በሌላ አነጋገር እኛ ያመንን በተቆጠረው የክርስቶስ ጽድቅ ከኃጢአትና ከሞት ኃይል ነፃ ወጥተናል፣ እናም አሁን በእግዚአብሔር ፊት፣ 'ከቶ ኃጢአትን እንዳልሠራሁ'፣ የተቤዠን እና በሰማይ የታሰረን ነን።  አሁን ግን ከጸደቅን እና ከእግዚአብሔር ጋር ከታረቅን በኋላ የመዳናችን የመቀደስ ክፍል መንቀሳቀስ አለበት እና ተግባራዊ የሆነ ስራ 'በህይወቱ ሊያድነን' መጀመር አለበት።  ‘ተግባር’ ሥራ እያልኩ ስናገር ይህ አቋም አይደለም ማለትም  ጸድቀናል ስንል አንድ ጊዜ የተደረገ ወይም በሰማይ የተደነገገ ማለት ነው።  ተግባራዊ ማለት እዚህ በአሁኑ ጊዜ፣ በምድር ላይ እና በምድራዊ ህይወታችን ውስጥ መሆን ያለበት ነገር ነው።  ሮሜ 1-4 ስለ አቋማችን ማረጋገጫ ነበር።  ሮሜ 5 ይህንን ያጠቃለለ እና ይህንን በኢየሱስ ሕይወት የሚገኘውን ተግባራዊ መዳን ያስተዋውቀናል።  ከዚያም ወደ ሮሜ 6 እስከ 8 ስንገባ ጳውሎስ ስለ ስለ አሁን መፅደቃችንን መዳናችን  ይናገራል ክፍል 2 በነገው እለት ፖስት አደርጋለሁ። ፀጋ ይብዛላችሁ ወንድማችሁ ይሳቅ 

ጳውሎስ ለማስተማር ሲሞክር ጌታውን አልታዘዘም ነበር።

ምስል
 እንዲህ ብለን እንጀምር ጳውሎስ ለማስተማር ሲሞክር ጌታውን አልታዘዘም ነበር (ማቴዎስ 23: 8-10) እና በክርስቶስ ተልእኮ እና መንግሥት ላይ ከማንም በላይ ጉዳት አድርሷል ምክንያቱም ሁሉም "የሚባሉት የጳውሎስ መልዕክቶች እና የክርስቶስ የምድር  ትምህርት አንድ አይነት አይደሉም!!! ስለዚህም ችግሩ ያለው ከጳውሎስ ነው ወይስ ያልገባን መፅሀፉን አንባቢዎች ነን??? መልሴ፡-   አብዛኞቹ “የሚባሉት” የክርስትና ሃይማኖቶች የመንግሥቱን ወንጌል (ትምህርት) ያስተምራሉ እና ጳውሎስን መልዕክቶች ችላ ይላሉ።  ሁሉም ሰባኪ የአራቱ ወንጌሎች ያስተምራል  እናም አልፎ አልፎ ካልሆነ ከጳውሎስ መልእክቶች ማስተማር ብዙ አይደፈርም ይህም በእውነቱ ዛሬ ለክርስቶስ አካል  ትምህርት ነውን ??? ኢየሱስ (እና 12ቱ) ሐዋርያት ያስተማሩት አራቱ ወንጌሎችና የመንግሥቱ ወንጌል መልእክት ለእስራኤል ትምህርት ነው።  እሱም ለአይሁዶች እና ምድራዊ መንግስት ዓላማ እና ርስታቸው በምድራዊው የሺህ ዓመት መንግሥት ውስጥ የተለየ ትንቢታዊ ትምህርት ነው።  ኢየሱስ በምድር የመጣው ለአይሁዶች ብቻ መሆኑን የሚያረጋግጡትን ቅዱሳት መጻህፍት አስተውሉ፡- ማቴዎስ 15፡24 እርሱ ግን መልሶ፡— ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ። ማቴዎስ 10፡5-6 እነዚህን አሥራ ሁለቱን ኢየሱስ ላካቸውና አዘዛቸው፡— በአሕዛብ መንገድ አትሂዱ፥ ወደ ሳምራውያንም ከተማ አትግቡ፤ (6) ነገር ግን ወደ ጠፉት በጎች ሂዱ እንጂ። ይህመሰ  ለእስራኤል ማለት ነው ግልፅ ነው። ሮሜ_15፡8 አሁንም ለአባቶች የተሰጠውን የተስፋ ቃል ያጸና ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እግዚአብሔር እውነት የመገረዝ አገልጋይ ነበረ እላለሁ። እንግዲ...