ክፍል 2: የተቀደሰ (በህይወቱ የዳነ)
'በህይወቱ የዳነ' ለኃጢአት ለመሞት እና ለአዲስ ሕይወት የማነፅ ሂደታዊ (ተራማጅ) ሥራ ነው ሮሜ 6፡4 ። እንደ መጽደቅ ያለ ፈጣን የቅፅበት ልውጠት ሳይሆን አእምሮን የማስተማር እና የማደስ ሂደት ነው። እሱም በትክክል የተከፋፈለውን የእግዚአብሔርን ቃል ማጥናት እና ከትምህርታችን ጋር በጳውሎስ ሥርዓተ ትምህርት ከሮሜ እስከ 2ኛ ተሰ በሥጋችን ያለው ኃጢአት ባህሪ ይገፈፍ ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን። ለጽድቅ እንድንሰጥ ራሳችንን ለኃጢአት እንደሞትን ልንቆጥር ይገባናል። በአዲስ ህግ ስር መኖር እና መስራት እንድንችል በክርስቶስ አካል ለህግ የሞትን መሆናችንን ማወቅ አለብን። ለእግዚአብሔር በመንፈስ አዲስ ፍሬ እናፈራ ዘንድ የሕይወት መንፈስ ሕግ ይገዛናል። በሕይወቱ የዳነ በክርስቶስ ከሕፃንነት ወደ እግዚአብሔር ልጅ የማደግ ሂደት ነው። ትምህርቱን በመረዳት እና ወደዚያ የፍቅር እየተጋን የመንፈስ ፍሬ በእኛ እንዲሰራ የመፍቀድ የእምነት ስራ ነው።
ፀጋ ይብዛላችሁ 🥰🙏
ወንድማችሁ ይሳቅ
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ